1.3 የግል ንጽህናችንን እንጠብቃለን
የግል ንጽህናችንን መጠበቅ ማለት ዘወትር የሰዉነታችንን፣የጸጉራችንን፣የምንለብሳቸዉን ልብሶች ንጽህና መጠበቅ ማለት ነዉ፡፡ሁላችሁም የግል ንጽህናቹን ትጠብቃላቹ አይደል? ጎበዞች!እስኪ አሁን ደግሞ
ሀ.የግል ንጽህናችንን ለምን እንደምንጠብቅ እንመልከትየግል ንጽህናችንን መጠበቅ፦
• ራሳችንን ከበሽታ ለመከላከል
• ንቁና ደስተኛ ሆኖ ለመገኘት
• ትምህርታችንን እና ስራችንን በትጋት ለማከናወን ይረዳናል፡፡
የግል ንጽህናችንን ካልጠበቅን ደግሞ፦
• ሰዉነታችን መጥፎ ሽታ ይኖረዋል
• ለተለያዩ በሽታዎች እንጋለጣለን ለምሳሌ፡- የዓይን ማዝ፣ወስፋት፣ኮሌራና የመሳሰሉት ናቸው፡፡
• የተለያዩ ተባዮች በጸጉራችንና በልብሳችን ዉስጥ እንዲፈጠሩ ያደርጋል፡፡ተማሪዎች የግል ንጽህና መጠበቅ ያለዉን ጠቀሜታ ተገነዘባችሁ አይደል ስለዚህ ሁላችሁም የግል ንጽህናቹን መጠበቅ አለባችሁ ማለት ነዉ፡፡
ለ. በግል ንጽሕና ጉድለት ምክንያት የሚመጡ በሽታዎች
ከታች በምስሉ ላይ ከምትመለከቷቸዉ ልጆች የትኛዉ ነዉ የግል ንጽህናዉን በአግባቡ የሚጠብቀዉ?በንጽሕና ጉድለት የሚመጡ በሽታዎች እንደ እከክ፣የዓይን ማዝ፣ወስፋት፣ኮሌራና የመሳሰሉት ናቸው። አይንን በቆሻሻ እጅ መንካት ለዓይን ማዝ በሽታ ይዳርጋል።
ሐ. ኤች አይ ቪ/ኤድስ
ኤች.ኢይ.ቪ/ኤድስ ከእንግሊዚኛ (HIV/AIDS) የተወሰደ ምኅጻረ ቃል ነው። ኤድስ ኤች.አይ.ቪ ከሚባል በዓይን የማይታይ ጥቃቅን ህዋሳት አማካኝነት የሚመጣ በሽታ ነው። የሰዉነታችንን በተፈጥሮ በሽታን የመከላከል አቅም የሚያዳክም በሽታ ነዉ፡፡ተማሪዎች ኤች አይ ቪ ኤድስ በምን እንደሚተላለፍ ታውቃላቹ?ኤች አይ ቪ ኤድስ ከሚተላለፍባቸዉ አንዱ በደም ንክኪ ነዉ፡፡ ለምሳሌ በሽታዉ ያለበት ሰዉ ደም ወደ ጤነኛዉ ሰዉ ደም ዉስጥ ሲገባ ሊተላለፍ ይችላል፡ ስለዚህ ተማሪዎች
መርፌ፣ምላጭና ሌሎች ስለታማ ነገሮችን በጋራ መጠቀም የለብንም፡፡
በምንጫወትበት ጊዜ ድንገተኛ አደጋ ሲከሰት ከደም ንክኪ መቆጠብ አለብን፡፡
አደጋዉ የደረሰበት ሰዉ የህክምና እርዳታ እንዲያገኝ ለሌሎች ሰዎች ማሳወቅ አለብን፡፡
ተማሪዎች ከታች የምትመለከቷቸዉ ልጆች ምን እያደረጉ ይመስላችኋል? ሁላቹም በደንብ ለማስወተዋል ሞክሩተማሪዎች! ዘወትር ጠዋት ከእንቅልፋችን ስንነሳ፡-
ፊታችንንና እጆቻችንን በዉሃና ሳሙና መታጠብ አለብን፡፡
እጆቻችንን ምግብ ከመመገባችን በፊትና በኋላ፣ከመጸዳጃ ቤት ስንወጣ፣ከጨዋታ መልስ፣ስራችንን ካጠናቀቅን በኋላ፣ማንኛዉም እንስሳ ከነካካን ቦኋላ በደንብ በሳሙናና በዉሃ መታጠብ አለብን፡፡
የአፋችንን ንጽህና ለመጠበቅ ሁል ጊዜ ጠዋት ከእንቅልፋችን ስንነቃ በጥርስ ብሩሽ ማጽዳት፣ምግብ ከተመገብን ቦኋላ በዉሃ መጉመጥመጥ አለብን፡፡
ንጹህ አካባቢ ለጤናችንና ለኑሮአችን ተስማሚ ስለሆነ ልብሳችንና አካባቢያችንን በንጽህና መያዝ አለብን፡፡
ዘወትር ማታ ወደ መኝታ ከመሄዳችን በፊት እግሮቻችንን መታጠብ አለብን።ገላና ፀጉርን መታጠብ ስንጫወት ወይም የተለያዩ ከባድ ሥራዎችን ስንሠራ ሰውነታችንን ያልበናል። ሰውነታችንን ሲያልበን መታጠብ አለብን። ካልታጠብን ሰውነታችን መጥፎ ጠረን ይፈጥራል። ፀጉራችንንም መታጠብና ማበጠር ያስፈልጋል። ፀጉራችን የማይበጠር ከሆነ ደግሞ ተባይ ሊፈጥር ይችላል። የአፋችን ንጽህና መጠበቅምግብ ከተመገብን ቦኃላ አፍን በውሃ መጉመጥመጥ ያስፈልጋል።እንዲሁም ጥርሳችንን ዘወትር ጠዋት ከመኝታ እንደተነሳን በጥርስ ቡርሽ መቦረሽ ወይም በእንጨት መፋቂያ መፋቅ ያስፈልጋል።አፋችን የማይጸዳ ከሆነ፦
• የአፋ ጠረን መጥፎ ይሆናል
• ጥርሳችን ለመቦርቦር ይጋለጣል። ይህም ለከፍተኛ የጥርስ ህመም ያጋልጣል።
• የጥርሳችን ቀለም ይቀየርና የጥርሳችንን ውበት ይቀንሳል። የልብስ ንጽሕናን መጠበቅልብሳችንን፡-በአግባቡ መልበስና በንጽሕና መያዝበሚቆሽሽበት ጊዜ ማጠብ ተኩስንና አጥፈን በንጽሕ ቦታ ማስቀመጥ ያስፈልጋል።
የአከባቢንጽሕናን መጠበቅንጹሕ አካባቢ ለጤናችን፣ለኑሮችንና ለትምህርታችን በጣም ጠቃሚ ነው።አካባቢያችን ንጹሕ እንዲሆን፡-
• መማሪያ ክፍላችንን ማጽዳት
• ቆሻሻዎችን በቆሻሻ መጣያ ሥፍራ (ቅርጫት ውስጥ) መጣል
• በመጸዳጃ ቤት በአግባቡ መጸዳዳት
• የቤት እንስሳት ከሰው መኖሪያ ቤት አከባቢ ራቅ ባለ ሥፍራ እንዲኖሩ ማደረግ
• የትምህርት ቤታችንንና የመኖሪያ አከባቢያችንን ጽዳት በጋራ መጠበቅ
• የአከባቢያችንን አትክልቶች መንከባከብ ያስፈልጋል።ተማሪዎች በዚህ ርዕስ የተማርናቸው
ምግብ በሕይወት ለመኖር ከሚያስፈልጉ ነገሮች አንዱ ነው።
ምግብ ከእንስሳትና ከተክሎች እናገኛለን።
የገበታ ሥርዐት ምግብ በምንመገብበት ወቅት ማድረግ ያለብን ሥነ ሥርዓት ነው።
ጤና ማለት አካላዊ ፣አእሮአዊና ማኅበራዊ ደኅንነት ነው።
የተሟላ ጤንነት ያለው ሰው ጠንካራና ጤነኛ ነው። ሕመምተኛ ሰው ግን ደካማና ፈዛዛ ነው።
ማንቀጥቀጥ፣ራስ ምታት፣ውጋትና ቁርጥማት፣ትኩሳት፣ማስታወክ፣ተቀማጥ፣የምግብ ፍላጎት መቀነስ ዋና ዋና የህመም ምልክቶች ናቸው፡፡
በማንኛውም ጊዜ የህመም ሰሜት ሲሰማን ለመምህራችን፣ለወላጆቻችን ወይም በአቅራቢያችን ለሚገኝ ሰው መናገር ይገባናል፡፡
የግል ንጽህናን መጠበቅ ለበሽታ የመጋለጥ እድልን ይቀንሳል፡፡
እከክ፣ወስፋት፣የዓይን ማዝ፣ ኮሌራ ወዘተ በንጽህና ጉድለት የሚመጡ በሽታዎች ናቸው
አች አይ ቪ/ ኤድስ በደም ንክኪ ይተላለፋል፡፡